Thursday, September 22, 2016
የ 2014–2015 የመርሀ ግብሮች እና የሪሶርሶች የቤተሰብ መመሪያ ስናቀርብላችሁ በጣም ደስ እያለን ነው። ይህ መመሪያ የተዘጋጀው እክል ላለባቸው ለዲስትሪክቱ ተማሪዎች በሙሉ፣ ስለምናካሂዳቸው ፕሮግራሞች ቁልፍ የሆኑ መረጃዎችን ለእናንተ ለማቅረብ ነው።
ራእያችን ዲስትሪክቱ፣ እክል ላለባችው ተማሪዎች የምርጫ ትምህርት ቤት ዲስትሪክታቸው እንዲሆን ለማድረግ ነው። ይህንን ማኅበረ ሰብ፣ በአዲስ መርሀ ግብሮች፣ ጥራት ባላቸው መምህራን እና ሠራተኞች፣ እንዲሁም ወላጅን በሚያሳትፉ እንቅስቃሴዎች አማካይነት ለማግልገል እንፈልጋለን። የልዩ ትምህርት አገልግሎቶቻችንን (special education services) እያሻሻልን እና እያጎለበትን በምንጓዝ በት ወቅት፣ ወላጆች በተጨማሪ ውቅታቸውን የጠበቁ መረጃዎች እንዲያገኙ እና በሂደቱም የተሳትፎ ድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ከፍ ተኛ ጥረት እያደረግን ነው።
ይህም ማለት ከእርስዎ ለመስማት እንወዳለን። እባክዎን ለሚኖርዎት ጥያቄዎች የልዩ ትምህርት አሰጣጥ ጽሕፈት ቤት (Office of Specialized Instruction (OSI)) ቡድን አባላትን ለማነጋገር አያመንቱ። ከእያንዳንዱ መርሀ ግብራችን እና ድጋፍ ሰጪዎቻችን ጋር የመገናኛ መረጃዎች ከዚህ መመሪያ ጽሑፍ በስተጀርባ ላይ ይገኛል።